Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Monday
Sep 08th
Home
Headline
  • Pause
  • Previous
  • Next
1/10
“ዳሽን ቢራ የመደራጀት መብትንና…
“ዳሽን ቢራ የመደራጀት መብትን የፕሬስ ነጻነትን ጥሷል”
የምግብ፣ የመጠጥ፣ የትምባሆና የመሳሰሉት ሠራተኞች ማኅበራት ፌዴሬሽን

- ለሪፖርተር ጋዜጣ መግለጫ በመስጠታቸው የማኅበሩ ሊቀመንበር ታስረው ነበር

በተሾመ ንቁ

የምግብ የመጠጥ፣ የትምባሆና የመሳሰሉት ሠራተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን የዳሽን ቢራ ፋብሪካ አመራር የሠራተኛ ማኅበር የመደራጀት መብትና የፕሬስ ነጻነትን የሚጥስ ተግባር ማከናወኑን አስታወቀ፡፡ ፋብሪካው ለሪፖርተር ጋዜጣ መግለጫ ሰጥተሃል ያላቸውን የሰራተኛ ማህበር ሊቀመንበር በፖሊስ አሳስሯል፡፡
Read more...
 
Zena
በመርካቶው ፍንዳታ የሟቾች...
በመርካቶው ፍንዳታ የሟቾች ቁጥር እየጨመረ ነው

በታምሩ ጽጌ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የድሮው ቀበሌ 30 በአዲሱ ቀበሌ 13/15 ወደ አመዴ ማዞሪያ ፊት ለፊት ወደ አውቶብስ ተራ በሚያስኬደው መንገድ አዲስ ከተማ ትምህርት ቤት መዳረሻ በመደዳ የተደረደሩት ሙሉ ባርና ሬስቶራንት፣ አምባሰል ሙዚቃ ቤት፣ አምባሰል የልብስ ስፌት ቤት፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ፎቶ ሻርፕና ዕድገት ኤሌክትሮኒክስ ይገኛሉ፡፡
Editorial
Image ገንዘብ ሲናገር ፍትሕ ዝም ይላል!
ገንዘብ እየተናገረ ነው፡፡ መናገር ብቻ ሳይበቃው እየፎከረ፣ “አካኪ ዘራፉን እየደቀደቀ፣ “ማን አለኝ ከልካይ” እያለ ነው፡፡ እየጮኸ ነው፡፡ ገንዘብ አፍ አውጥቶ ሲጮህ፣ ፍትህ ይሸበባል፡፡ ዝም ማለት ብቻ ሳይሆን፣ ይርበተበታል፡፡ ይሽቆጠቆጣል፡፡ የሚያሳፍረውና የሚያስፈራውም ይኸው ነው፡፡ ገንዘብ ሲያንባርቅ ፍትሕ የብረት ልጓም ይሰነቀርበታል፡፡ እንዲያ ሲሆን ይርዳል፡፡ ኤሎሄ ኤሎሄ፣    ኆገንዘብ ነህና እግርህ ስር ወድቄ እሰግዳለሁነ፣ ብሎ ከገንዘብ እግር ላይ ወድቆ ፍትሕ ስቅስቅ ብሎ እንዲያለቅስ ይደረጋል፡፡ በአገራችንም ይኸው ድርጊት እየታየ መሆኑን መናገር ይቻላል፡፡
 
Politics
ዘመን 2000 - ቀውስ እና ሕዳሴ
በጌታቸው ንጋቱ

በኢትዮጵያውያን የዘመን አቆጣጠር ስሌት አዲስ ዓመት፣ አዲስ ምዕተ ዓመትና አዲስ ሺህ ዓመት (ሚሌኒየም) ከገባ አንድ ዓመት ሆነው፡፡ ለሚሌኒየሙ መቀበያ አገሪቱ ከጫፍ እስከ ጫፍ በሚሌኒየም ጽ/ቤቶች ተዋቅራ ብዙ ሥራዎች ሲሰሩ ከርመዋል፡፡ ሥራዎቹና የአዲሱ ሚሌኒየም መባቻም በብዙ ተስፋዎችና የሚያማምሩ ቃላት የተዋቡ ነበሩ፡፡ ሁሉንም ተስፋና አዲስ ራዕይ በአንድ ላይ የያዘ አንድ ቃልም በአገሪቱ ከዳር እስከ ዳር አስተጋብቷል፡፡ ሕዳሴ (Renaissance) የሚለው ቃል ለብዙዎች አዲስ ቢሆንም ትርጉሙ በደምሳሳው ከወደቁበት የመነሳት፣ በአዲስ መንፈስ የመመራትና ታላቅ ሕዝብና አገር የመሆን ፍላጎትና ተነሳሽነትን የሚያመለክት ነው፡፡
Briefs
ሦስት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጆች...

ሦስት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጆች ከ6ሺ በላይ ተማሪዎችን አስመረቁ

በትምህርት ሚኒስቴር በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ሙሉ ዕውቅናን አግኝተው ማስተማር ከጀመሩት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጆች መካከል ሦስቱ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጆች ከ6 ሺ በላይ ተማሪዎችን አስመረቁ፡፡

 

 
Business & Economy
ደደቢት ቅርንጫፎቹን እያስፋፋ ነው
በብርሃኑ ፈቃደ

የኢትዮጵያ ገጠር ልማት ስትራቴጂ የግብርናውም ሆነ የሌሎች ሴክተሮችን ልማት ለማምጣት የገጠር ፋይናንስ አገልግሎት መጐልበት እንዳለበት ይገለፃል፡፡ የገጠር ፋይናንስ አገልግሎት መስፋፋት ለግብርና ምርታማነት፣ ለኢንቨስትመንት፣ ለሥራ መፈጠርና ለግብርና ግብአቶችና ውጤቶች ገበያ ኖሯቸው እንዲጐለብቱ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ የአነስተኛ ብድር ተቋማት ማኅበር መረጃ ይጠቁማል፡፡
Shemach
ገበያና ሸማች ለየቅል
(በአብርሃም ግሩም)

በአገራችን የተከሰተው የዋጋ ንረት አሁንም ልጓም አልባ ይመስላል፡፡ በዝቅተኛና በመካከለኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኘው ሕዝብ የሚቋቋምበት ጫንቃው ዝሎ እየተውተረተረ ይገኛል፡፡
 
Interview
“የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ችግር...
“የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ችግር ቴክኒክ ክፍሉ ነው ከተባለ ይምጡና እንነጋገር”

ሻም/ዱቤ ጅሎ

የፌዴሬሽኑ ቴክኒክ ክፍል ኃላፊ

በቤጂንግ ኦሊምፒክ የኢትዮጵያ ቡድን ያስመዘገበውን ውጤት ተከትሎ፣ በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ላይ በርካታ አስተያየቶች እየተሰጡ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በቤጅንግ ኦሊምፒክ ሜዳሊያ ሰንጠረዥ ውስጥ የገባችው በፌዴሬሽኑ ጥረት ሳይሆን፣ በአትሌቶች የግል ጥረት መሆኑ በስፋት ይነገራል፡፡ ይህንኑ ተከትሎ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ብሔራዊ አሰልጣኞችን አሰናብቷል፡፡ እነዚህንና ሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮችን በማካተት የፌዴሬሽኑን ቴክኒክ ክፍል ኃላፊ ሻምበል ዱቤ ጅሎን ደረጀ ጠገናው አነጋግሯቸዋል፡፡
Fermata
ዋሽንግተን ፓስት
ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ ከሄድኩባቸው የጋዜጣ ክፍሎች ሁሉ የማረከኝ “ዋሺንግተን ፖስት” ጋዜጣ ቢሮ ነው፡፡ ቢሮ ስላችሁ እንደ እኛ አገር የጋዜጣ ቢሮዎች (የመንግሥትም የግልም ማለቴ ነው) በአይን የሚቆጠር ድምር ያለው ሠራተኛ የሚገኝበት አይደለም፡፡
 
Kibur Minister
ክቡር ሚኒስትር - ሃሎ! ክቡር ሚኒስትር፣
- እሺ፣ ምን አዲስ ነገር አለ? በዛ ጉዳይ ዙሪያ?
- ቶሎ ብለን አንድ እርምጃ መውሰዱ አስፈላጊ ይመስለኛል፡፡
- አንተ ሰውዬ እንዲህ ዓይነት ነገር በስልክ አትናገር አላልኩህም፡፡ በል አሁን በአስቸኳይ ወደዚያ ቦታ እለፍና እንገናኝ
Life & Art
ጉራጌን በ"ዮኸምያ ክትፍወ...

ጉራጌን በ"ዮኸምያ ክትፍወ በጉየ ተኸራር"
በሔኖክ ያሬድ

"ኢትዮጵያ ሀገሬ መመኪያዬ ክብሬ" የሚለው ዘፈን እያቀነቀንኩ ነበር፡፡ ነሐሴ 25 ቀን 2000 ከዮኸምያ በጉየ ተኸራር የጉራጌ የባህል ማዕከል የወጣሁት፡፡ ዘፈኑ እንዴት እንደመጣልኝ ይገርመኛል፡፡ ሞዛይክ ከምትባለዋ ሁሉንም አሰባስባ ከያዘችው ኢትዮጵያ አንዱ ገጽታ ጉራጌ ውስጥ ገባሁ፡፡

 

 
Social
የወባ በሽታ መቀነስ ኅብረተሰቡን...
የወባ በሽታ መቀነስ ኅብረተሰቡን እያዘናጋ ነው

በታደሰ ገብረማርያም

ኢትዮጵያ ውስጥ ለሞት የሚዳረጉ ከፍተኛ የጤና ችግሮች ናቸው ተብለው በዝርዝር ከተቀመጡት አሥር በሽታዎች መካከል በመጀመሪያ ደረጃ ላይ የሚገኘው የወባ በሽታ ነው፡፡ ከሁለትና ሦስት ዓመታት ወዲህ ግን ይህ ዓይነቱ በሽታ እየቀነሰ መጥቷል፡፡ በቀጣዩ ዘመንም ፍፁም የማስወገድና የማጥፋት ትልም ይኖራል ተብሎ መታመኑን በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የወባና ሌሎች ቬክተር ወለድ በሽታዎች መከላከያና መቆጣጠሪያ በድን መሪ ገለፁ፡፡ የኦሮሚያ፣ የአማራ፣ የጋምቤላና የደቡብ ብሄር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች የወባ ባለሙያዎች ደግሞ የበሽታው መቀነስ ሕብረተሰቡ በአጎበር አጠቃቀም ላይ እንዲዘነጋ ማድረጉን አስታወቁ
Science & Technology
Image ሽቶ ላልተወለዱ ልጆች አደገኛ ነው
ወደፊት ለሚወለድ ልጅ የመጀመሪያዎቹ ሦስት የእርግዝና ወራት እጅግ ጥንቃቄ የሚያስፈልጋቸው ሲሆኑ በእነዚህ ወራት ሽቶ እና መሰል መዓዛ ያላቸውን ቅመሞች የሚጠቀሙ እርጉዝ ሴቶች ወደፊት የሚወልዱትን ወንድ ልጅ ለመሃንነት ሊዳርጉት እንደሚችሉ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
 
Diaspora
“ሁለት መቶ ዶላር” ብቻ ይዘው...
“ሁለት መቶ ዶላር” ብቻ ይዘው የተመለሱት ዲያስፖራ

በዳዊት ታዬ

“ከኢትዮጵያ መልቀቅ እንዳለብኝ ስወስን መጀመሪያ የታየኝ ጅቡቲ መሄድ ነበር፡፡ ጅቡቲን የመረጥኩበት ምክንያት እስካሁን ድረስ አላውቅም፡፡ በተሰደድኩበት ወቅት ብሔራዊ ውትድርና ቁም ስቅላችንን ያሳየን ስለነበር ይህንን ሸሽቼ ከአዲስ አበባ ድሬዳዋ ሄድኩ፡፡ ከድሬዳዋ በአትክልት ባቡር ተጭኜ ጅቡቲ ድንበር ድረስ ተጉዤ ከድንበር ጅቡቲ ከተማ ድረስ በእግሬ ገባሁ” በማለት ስደቱ እንዴት እንደነበር የገለፁልን አቶ ዳንኤል ክፍሌ ናቸው፡፡
Youth
Image የሥነ ተዋልዶ ጤና በከፍተኛ...
የሥነ ተዋልዶ ጤና በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት

በምህረት አስቻለው

የስነተዋልዶ ጤና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምን ይመስላል? ከሥነ ተዋልዶ ጤና ጋር በተያያዘ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ያሉባቸው ችግሮች ምንድን ናቸው? የሚሉትና ሌሎችም ተመሳሳይ ጥያቄዎች "የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን የሥነ ተዋልዶ ፍላጐትና መብት መመልከት የሁለም ሰው ኃላፊነት ነው" በሚል ርዕስ ነሐሴ 22 ቀን 2000 በግዮን ሆቴል በተካሄደው ብሔራዊ የከፍተኛ ተቋማት የሥነ ተዋልዶ ጤና ሁኔታ ኮንፈረንስ ተዳስሰዋል፡፡

 
Opinion
Image የዋና አዘጋጁ እስር ሌሎችንም ይነካካል

ሃብታሙ በቀለ

ያለፈው ሳምንት ሃገረኛዎቹና የውጭ ሚዲያ ጭምር ሰፊ ሽፋን የሰጡት የሪፖርተር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ፣ ከሕግ ውጭ በሆነ አያያዝ ተገዶ ወደ አማራ ክልል ፖሊስ ጣቢያ ተወስዶ፣ የመታሰሩን ዜና ነበር፡፡ በሪፖርተር ጋዜጣና በሌሎች የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪዎች ድረ ገፅ ላይ በስፋት የተተነተነበት የክልሉ ፖሊስና ፍርድ ቤት "አያገባቸው ገብተው አያወዛቸው ተቀብተው" ያለ ሥልጠናቸውና ያለመብታቸው መብት መድፈር ሕገ ወጥነት መሆኑም ሲጠቀስ ሰንብቷል፡፡

 

Letter to Reporter
የድርጅቱን ገንዘብ የዘረፉ ሕግ ፊት ይቅረቡ
በሪፖርተር ጋዜጣ ነሐሴ 25 ቀን 2ዐዐዐ “የፖስታ አገልግሎት ድርጅት በሠራተኞቹ እየተዘረፈ ነው” በሚል ርዕስ የወጣው ዜና ድርጅቱ ከፍተኛ ዝርፊያ እየተፈፀመበት መሆኑን ያሳያል፡፡ ይህንን እኩይ ተግባር የፈፀሙ ሠራተኞች ከያሉበት ታድነው ሕግ ፊት ቀርበው ተገቢውን ቅጣት ማግኘት ይኖርባቸዋል፡፡
 
Women
እንዲህም ይጎበዛል

ከሁለት ሴት ልጆቻቸው ጋር በመሆን የተለያዩ ሥልጠናዎችን የሚያዘጋጅና ጥናቶችን የሚያደርግ ኤንታክ (NTAC) ኢንተርናሽናል የተባለ ድርጅት አቋቁመዋል፡፡ ሁለተኛ ልጃቸው የድርጅቱ ዳይሬክተር፣ እሳቸው ደግሞ ምክትል፣ የመጀመሪያ ልጃቸው ደግሞ የውጭ ግንኙነት ሆና በመሥራት ላይ ይገኛሉ፡፡

 

Temuaget
"ዓባይ መነኰሰ"፣ "ተከዜ አረጀ አሉ"...

"ዓባይ መነኰሰ"፣ "ተከዜ አረጀ አሉ" እንጉርጉሮ እንዲቀር"
በፍሥሐ ገብረ ኪዳን

የዓባይ ድልድይ በያዝነው የ2000 ዓመት መሰናበቻ ጳጉሜ ወር መጨረሻ ላይ እንደሚመረቅና "ሕዳሴ" የሚል ስም እንደሚሰጠው፣ በምረቃውም ዕለት ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት እንደሚገኙ የዘገበው የሪፖርተር ጋዜጣ የነሐሴ 25 ቀን ዜና ማንበቤን ተከትሎ ነው በዚህ ጉዳይ ላይ አንዳንድ ጉዳዮችን ለምን አላነሳም ብዬ የወሰንኩት፡፡ በጃፓናውያን ድጋፍና ወጪ የተሰራው ድልድይና መንገድ የሚመረቀው ገና ጳጉሜ 5 ቀን ቢሆንም ሕዳሴ የሚል ስያሜ እንደሚሰጠው የመገለጹ ወሬ እውነት ከሆነ በምረቃው ሥነሥርዓት ላይ የሚገኙትን ባለሥልጣናት ከፍተኛነትና ምናልባትም ማንነት እሱ ራሱ ብቻውን ያመለክታል ብዬ እጠረጥራለሁ፡፡

 

 
Law
የአካል ጉዳተኞች የሥራ...

የአካል ጉዳተኞች የሥራ ስምሪት መብት አዋጅ
በሰለሞን ጎሹ

በ1986 ዓ.ም. የወጣው የአካል ጉዳተኞች የሥራ ሥምሪት መብት አዋጅ ቁጥር 101/1986 ከ14 ዓመታት ቆይታ በኋላ እየተገባደደ ባለውና በያዝነው ዓመት መጋቢት ወር በ"የአካል ጉዳተኞች የሥራ ሥምሪት መብት አዋጅ ቁጥር 568/2000" ተሽሯል፡፡

 

Zennk
አኩሪ ሥራ ሠርተው ያለፉ

የማታ ማታ ብዙ ሰዎች ለርጅና እጅ ሳይሰጡ ለአገራቸው እንዲሁም ለሌላውም ህዝብ አያሌ ጠቃሚ ነገር አበርክተው እንዳለፉ ትሪካቸው ያስረዳል፡፡ ለምሳሌ ከብዙ በጥቂቱ የሚከተሉት ሰዎች በአራያነታቸው ይጠቀሳሉ፡፡

 

 
Delalaw
ጫማ የሰቀሉ
“ፊጋ” በሬ፡፡ በሬው ፊጋ ሆኗል እያሉ የሰንጋ ተራ ወሬ ያመጡልኛል፡፡ ደንባራ በሬ፡፡ ድንብርብር ብሎ ሰውን የሚያስደነብር፡፡ ሮጦ የሚያስሮጥ፡፡ ፊጋ ሕይወት፣ ፊጋ በሬ፡፡ ፊጋ ገበያ፡፡
Teles
የደበዘዙ ስሜቶች

በምሕረት አስቻለው

ከአምስት ወራት በፊት የኩላሊትና የሳንባ ህመም እንዳለባቸው ተነግሯቸው የተለያዩ ሕክምናዎችን አድርገዋል፡፡ ነገር ግን ከሕክምና በኋላም ፈውስ ማግኘት አልቻሉም፡፡ አንድ ቀን ዘወትር ወደ ሆስፒታል ያመላልሳቸው የነበረው የመጀመሪያ ልጃቸው "እማዬ የኤች.አይ.ቪ ቫይረስ በደምሽ ውስጥ ቢኖር ምን ታደርጊያለሽ?" የሚል ድንገተኛ ጥያቄ አቀረበላቸው፡፡ ቫይረሱ በደማቸው ይገኛል የሚል ጥርጣሬ ፈፅሞ እንደሌላቸው፣ ቢኖርባቸውም መኖር እንደሚችሉ ለልጃቸው ይነግሩታል፡፡

 

 
Sport
"መንግሥት ጥፋተኛው ማን...

"መንግሥት ጥፋተኛው ማን እንደሆነ አጣርቶ ውሳኔ ይስጥ"
ዶክተር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ባለፈው ሠኞና ማክሰኞ 26 እና 27 ቀን 2000 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ በጉባኤው ከቀረቡት አጀንዳዎች መካከል አንዱ የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ፣ ከፊፋ እና ካፍ ጋር ስለነበረው ሁኔታ የሚመለከት ሲሆን፣ ጉባኤው ባለው ማንዴት መሰረት የቀረቡትን ሪፖርት በመመርመር ውሳኔ አሳልፏል፡፡

 

Taxi
ሳይደርቅ በእርጥቡ
በታክሲ ጉዞ ነጥብ በነጥብ ከተከታተሉ የሚመዘገብ ነገር ይበዛል፡፡ ለወሬና ለጽሑፍ የሚበቃ ርዕሰ ጉዳይ አይጠፋም፡፡ ነባር የታክሲ ደንበኞች ብንሆንም ብዙውን ጊዜ ከመመስገንና ከመከበር ይልቅ ብሽቀትን አትርፈን እንገባለን፡፡ በሌላው የሥራ ዘርፍ ደንበኝነት እንደሌሎች አገሮች ባያስከብርም “እንኳን ደህና መጣችሁ”፣ “የት ጠፋችሁ?” መባሉ አይጠፋም፡፡ በታክሲ አገልግሎት ግን ደንበኛ ንጉሥ ነው፤ ደንበኛ ቢሳሳትም ትክክል ነው የሚለውን የቢዝነስ መሳቢያ መርህ ተቀባይነት የለውም፡፡ “ይህ ሰው ዓመቱን በሙሉ በእኛ ታክሲ ነው የተጓጓዘው” ተብሎ የታሪፍ ቅናሽም ይሁን ጥሩ መስተንግዶ አይደረግለትም፡፡
 
World
የሪፐብሊካን ፓርቲ እጩ ምክትል....

የሪፐብሊካን ፓርቲ እጩ ምክትል ኘሬዚዳንቷ የቤተሰብ ጉዳይ ውዝግብ ፈጥሯል
በኃይሌ ሙሉ

ለአቅመ ሄዋን ሳይደርሱ የሚከሰት እርግዝና አሜሪካ ውስጥ የፖለቲካ ጉዳይ በሆነበትና የልጅ እናቶች ሥራ እንዲሰሩ መገደዳቸው የሞራል ክርክር እያስነሳ ባለበት በአሁኑ ወቅት የሪፐብሊካኑ እጩ ኘሬዚዳንት ጆን ማኬይን የአላሳካ ገዢ የሆኑትን ወ/ሮ ሳራ ፔሊን ምክትል ኘሬዚዳንት አድርገው መምረጣቸው ትልቅ ውዝግብ ፈጥሯል፡፡

 

 
  • Do You Know ?
    How To Increase Font Size
    You can increase the font size of the website if it appears smaller than normal. Just click the member area link at the top right of this page and the page will slide down. At the top left corner of the page, look for three small buttons. To increase font size, click the button with "+" sign and "-" sign to decrease font size.
  • Tips !
    Tips for Amharic Version
    • Use Internet Explorer version 6 or better
    • Adjust your screen resolution to 1024 X 768
    • Use the font resizer to increase font size if needed
    • Though it is not strictly needed having power geez unicode font could enhance the font rendering in your browser
 

Important Links

Visit Ethiopian Yellow PagesA forum on Dialogue, Democracy & Development